The Montgomery County Proclaims March as The Month of Adwa Victory

የማርች ወር የአድዋ ድል ወር ተብሎ እንዲታወስ ሞንትጎመሪ ካውንቲ አወጀ::  በሜሪላንድ ግዛት የሞንትጎመሪ ካውንቲ የማርች ወር የአድዋ ድል ወር ተብሎ እንዲታወስ አወጇል
According to Press release by the Ethiopian Heritage Society in North America, The Honorable Isiah Leggett, Executive, Montgomery County, MD has proclaimed the  Month of March as  Adwa VIctory Month”

The county in its proclamation acknowledges the importance of the Victory of Adwa as the landmark event for the liberation of the rest of Africa from colonization.

12803154_10153849227483950_6094949976388968353_n

ከኢትዮጵያውያን አልፎ ለመላው የአፍሪካ ሃገሮች እና ጥቁር ህዝቦች ሁሉ የነጻነት ቀንዲል የሆነውን የአድዋ ድል 120ኛ አመት በዓል የሞንትጎመሪ ካውንቲ ወሩን የአድዋ ድል ወር ተብሎ እንዲታወስ በተከበሩት የካውንቲው ተወካይ አይሳያ ሌጌት ተፈርሞ የወጣው አዋጅ በንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ ምኒሊክ እና እቴጌ ጣይቱ የተመራው የተባብረው የኢትዮጵያ ወታደር ወራሪውን የኢጣልያ ሃይል እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ማርች 01 1896 በአድዋ ላይ ያሸነፈበት ታሪክ የኢትዮጵያውያን አንድነት እና የአፍሪካ ሃገሮች ከአውሮፓ ቅኝ ግዛት ለመውጣት ለሚያደርጉት ትግል መነሻ የሆነ ታሪካዊ ቀን መሆኑን አዋጁ አስታውሷል::

አዋጁ በተጨማሪም ኢትዮጵያውያን በቁጥር በካውንቲው ከሚኖሩ ከአፍሪካ ከመጡ ነዋሪዎች በሁለተኛነት እንደሚገኙ እና ለካውንቲው የሚያደርጉትን አስተዋፅኦ አስታውሷል::

ይህ በየአመቱ የሚከበረው ታሪካዊው የአድዋ ድል በዚህ ታላቅ መልክ እንዲታወስ እና በታሪክም እንዲቀመጥ ያደረገው ተቀማጭነቱ በአሜሪካን ሃገር የሆነው የኢትዮጵያውያን ውርስ እና ቅርስ ማህበር በሰሜን አሜሪካ የተባለ ኢትዮጵያውያን ታሪካቸውን እና ባህሎቻቸውን ጠብቀው እንዲቆዩ የሚሰራ ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጅት ነው::

 

Source : Facebook courtesy of

Yohannes Ayalew

Related Posts

Leave a Reply

Read also x